BACK TO HOME PAGE BACK TO NEWS HIGHLIGHTS
 
     
     
     
 
 
 
 
   
OUR SURVIVAL DEPENDS ON OUR CUSTOMERS
EXTRACTED FROM MIDROC NEWSLETTER ISSUE NO. 20
MAY-JUNE 2004
DR. AREGA YIRDAW, CHIEF EXECUTIVE OFFICER, MIDROC ETHIOPIA  
 
     

«ፈገግታ የሌለው ንግድ ቤት አይከፈት» ይላሉ ቻይና­ዎች፤ በእኛም ሀገር «ከፍትፍቱ ፊቱ» የሚል አባባልም አለ፡፡ ይህ አባባል ተጨባጭ ዕውነታን መሠረት ያደረገ መሆኑን በዕለታዊ የሥራና የማኅበራዊ እንቅስቃሴያችን የምንገነዘበው ነው፡፡ በመሆኑም ደንበኞችን በመበዝበዝና በማንገላታት ሳይሆን በጥሩ ትህትናና በመልካም አቀባበል ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠትን ዋናው የሥራ መመሪያችን አድርገን በመተግበር ላይ እንገኛለን፡፡ ያለፉት ሦስት ዓመታት የሥራ ተሞክሮ እንደሚያሳየው ለደንበኛ ክብርን የሰጠ አያያዛችን ውጤትን አስገኝቶልናል፡፡

ለኩባንያዎ­ቻችን ዕድገት፣ መስፋፋትና ቀጣይነት ደንበኞች አስተማማኝ ዋስትና መሆናቸውን በሚገባ እናውቃለን፡፡ ስለዚህ ደንበኞች-ተኮር (Customer-Focused) የአሠራር መንገድን በመከተል ለሽያጭ የምናቀርበው ምርትና አገልግሎት ለደንበኞች እርካታን (Satisfaction) መስጠቱንና አለመስጠቱን በመከታተል እርካታን እንደመለኪያ (Yardstick) አድርገን መከተል መመሪያችን አድርገን ይዘናል፡፡ ዐቢይ ትኩረታችን የደንበኞችን ፍላጎት ማርካት በመሆኑ የምንሸጠው «እርካታን» ነው የሚል እምነት አለን፡፡

ለደንበኞቻችን ያለንን ክብር ለመግለጽ፣ የኩባንያ­ዎቻችን ሠራተኞች ከደንበኞች ጋር እንዲተዋወቁና ልምድ እንዲለዋወጡ ለማስቻል በየዓመቱ «ደንበኞች ቀን» ማክበር ባህላችን አድርገነዋል፡፡ በዘንድሮው «ደንበኞች ቀን» በዓል ላይ በርካታ ደንበኞቻችን ተሳትፈዋል፡፡ ለዕድገትና ለሕልውናችን ያላቸውን ጉልህ አስተዋጽዖ ለማስገንዘብ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ምርት ደንበኞቻችን የዋንጫና የሠርቲፊኬት ሽልማት አበርክተናል፡፡ ይህም በዓል የታሰበለትን ግብ የመታና ውጤታማ ነበር፡፡ በዓሉ የተሳካ እንዲሆን ጥረት ላደረጉት የኩባንያዎ­ ሠራተኞች፤ እንዲሁም ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር ጥሪያችንን አክብራችሁ ለተሳተፋችሁት ደንበኞቻችን ከፍተኛ ምሥጋናዬን አቀርባለሁ፡፡ «ደንበኞች ቀን» ማክበር ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ በመሆኑም ዕለቱን በየዓመቱ በተጠናከረ ሁኔታ ማክበሩን የምንገፋበት ይሆናል፡፡

  CEO'S MESSAGES ARCHIVES
     
All Contents © Copyright MIDROC Ethiopia, Office of the Chief Executive Officer, 2005. All Rights Reserved.