BACK TO HOME PAGE BACK TO NEWS HIGHLIGHTS
 
     
     
     
 
 
 
 
 
   
HAPPY ETHIOPIAN NEW YEAR!
1998 E.C. (2005/2006 G.C.)
EXTRACTED FROM MIDROC NEWSLETTER ISSUE NO. 27
JUL.-AUG. 2005
DR. AREGA YIRDAW, CHIEF EXECUTIVE OFFICER, MIDROC ETHIOPIA  
 
     

እን ከዘመነ-ማቴዎ ወደ ዘመነ-ማርቆስ በሰላም አሸጋገራችሁ! ሊቀመንበራችን ሼክ ሙሐመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ ለመላው የድርጅቶቻችንን ሠራተኞችና ቤተሰቦች አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የጤና፣ እና የብልጽግና እንዲሆንላችሁ ያስተላለፉትን መልዕክት ስገልጽ ከፍተኛ ደስታ እየተሰማኝ ነው፡፡

ለሀገራቸውና ለወገናቸው አለኝታ የሆኑት ሊቀመንበራችን እንዳለፉት ዓመታት ዘንድሮም በተለመደው ልግስናቸው የልዩ ችሮታ የአዲስ ዓመት በዓል «እንኳን አደረሳችሁ» የአንድ ወር ደመወዝ ክፍያ በመፍቀዳቸው በሲ.. ቢሮና በሥሩ የተደራጁት 11 ኩባንያዎ ውስጥ ያሉ ሠራተኞች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ ቅንነትና ደግነትን የተላበሱት ሊቀመንበራችንና ቤተሰቦቻቸው ለዘመን መለወጫ በዓል መዋያ ልዩ ስጦታ በማበርከታቸው የተሰማኝን አድናቆት በመላ ሠራተኞች ስም በአክብሮት እገልፃለሁ፡፡

በአዲሱ ዓመት መግቢያ ላይ ሆነን ያለፈው ዓመት የሥራ ሂደትና እንቅስቃሴያችንን ስንመለከት አበረታችና በጎ ጅምሮች የታዩበት ሆነው እናገኛለን፡፡ በአሁኑ ጊዜ በድርጅቶቻችን ውስጥ በተቀናጀ አመራር ስልት እየተመዘገበ ያለው ውጤት ለበለጠ ሥራ የሚያተጋ ነው፡፡ ለዚህ የስኬት ደረጃ ለመድረስ መላው ሠራተኛና አመራር ያበረከተው አስተዋጽዖ ደምቆ የሚታይ ሆኗል፡፡

በዘንድሮውም አዲስ ዓመት፣ በአዲስ መንፈስና በአዲስ ጉልበት በመንቀሳቀስ ውጥን ሥራዎቻችንን ለፍሬ ለማብቃት፤ የጀመርነውን ኩባንያዎቻችንን የማጠናከርና የማስፋፋት እንቅስቃሴ ከዳር ለማድረስ እጅ ለእጅ ተያይዘን በሕብረትና በመተሳሰብ እንድንሠራ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ፡፡

ቸሩ ፈጣሪያችን ለሊቀመንበራችን ለሼክ ሙሐመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ፣ ለወንድሞቻቸውና ለመላው ቤተሰባቸው፣ ለድርጅቶቻችን ሠራተኞችና መላው ቤተሰባቸው፣ በአጠቃላይም ለሀገራችን ሕዝብ ሰላም፣ ጤናና ብልጽግና እንዲሰጥልን ልባዊ ምኞቴን እገልጻለሁ፡፡ መልካም አዲስ ዓመት!

  CEO'S MESSAGES ARCHIVES
     
All Contents © Copyright MIDROC Ethiopia, Office of the Chief Executive Officer, 2005. All Rights Reserved.